fredag 11 december 2015

የአጋዚ ሰራዊት በምዕራብ አሪሲ አዳባ ከተማ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ – አንድ ወጣት መገደሉ ተሰማ

adaba
(ዘ-ሐበሻ) በምዕራብ አሪሲ አዳባ ከተማ ለሰላማዊ ሰልፍ በወጡ የህብረተሰቡ ክፍል ላይ የአጋዚ ጦር ወታደራዊ እርምጃ መውሰዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ:: በከተማዋ የአጋዚ ጦር በወሰደው እርምጃ የጥይት ድምጽ እና ጭስ ከተማዋን ሞልቶት እንደዋለ ነዋሪዎቹ አስታውቀዋል::
እንደ ነዋሪዎች ገለጻ ከሆነ በአዳባ ከተማ በአጋዚ ጦር በተወሰደው ወታደራዊ እርምጃ አንድ ወጣት ተገድሏል:: በአዳባ የተገደለው ወጣት ስም ነስረዲን መሀመድ እንደሚባልም ታውቋል::
በአሁኑ ሰዓት ወደ አዳባ ከተማ መግባትም ሆነ መውጣትም የማይቻል ሲሆን ወታደሮች ከተማዋን አጥረዋታል:: በአጋዚ ጦር ጥቃት የቆሰሉት ወገኖች በሃዋሳ እና ኩረያ ሆስፒታል እያታከሙ መሆኑም ተሰምቷል::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48998#sthash.gn7pTMza.dpuf

Inga kommentarer:

Skicka en kommentar