onsdag 16 december 2015

የቀድሞው ጠ/ሚ/ር ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የሰሞኑ ሕዝባዊ ቁጣ ለቤተሰቧና ለንብረቷ እንድታስብ እንዳደረጋት ገለጸች

የቀድሞው ጠ/ሚ/ር ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የሰሞኑ ሕዝባዊ ቁጣ ለቤተሰቧና ለንብረቷ እንድታስብ እንዳደረጋት ገለጸች 



azeb
(ዘ-ሐበሻ) በአንድ ወቅት “ደሃ ነኝ… ከዓለማችን የደሃ ሀገር መሪዎች መካከል እኛ አንደኞቹ ነን” ስትል የነበረችው የቀድሞው ሟች ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ሰሞኑን በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ በገንዘቧና በቤተሰቧ ላይ ያሳደረውን ስጋቷን በፌስቡክ ገጿ ገለጸች::
Screen Shot 2015-12-16 at 3.54.28 AM
ወ/ሮዋ በፌስቡክ ገጿ እንዳለችው “በሰሞኑ በሚሆነው ነገር በጣም በጣም የሚያሳዝን ነው። እኛ እንግዲህ አስራ ሰባት አመት ትግል ቦኅላ ለዚህ ድል በቅተን ደርግን ገርስሰን ለመላው ኢትዮጵያዊ ዲሞክራሲ ያለባት አገር መስርተናል። እና መለስ ልጅነቱን በሙሉ የለፋበትን አላማ ዛሬ በዚህ ብጥብጥ ባነሱ አደገኛ ቦዘኔዎች ከልማት ታቅበን መቀመጥ በጣም ያሳዝናል በእውነቱ። ስራ አቁሞ ሰልፍ ሲሰለፉ መዋል ምን ይባላል? ብንሰራ አይሻልም? እንደ የድሮ ስርአት ነፍጠኞች ያሁኑ አገር ባይበጠብጡ ይሻላል።”
ወ/ሮዋ አክላም ” ትልልቅ አዋቂ ሰዎች የመለስ አይምሮ ያፈለቀውን ራእይ የሚያስፈፅሙ አሉ ተመርጠው በህዝብ መቶ ድምፅ ተሰጥቷቸ እያሉ አሁን ለምን አገር ይረበሻል? እኔ በእውነቱ ከሆነ ለቤተሰብ ለንብረቴ ማሰብ ጀምሬያለሁ። እርግጠኛ ነኝ ብዙዎች እንደኔው ማሰብ መስጋት ጀምረዋል። ጥሩ አይደለም ሰላም እና መረጋጋት ያስፈልጋል በመጀመሪያ።” ብላለች::
ስለ ባሏ ራዕይ ከሞተ በኋላም እንዲነገር የምትፈልገው ወይዘሮ አዜብ ሕዝብ የመለስን ፓርክ በማቃጠሉ የተሰማትን ስሜት ስትገልጽም “የመለስ እሚያህል ትልቅ ሰው በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ እማይታወቅ ሰው፣ ከዚህ በፊትም እንዳልኩት በፔሮል የሚተዳደር ፕሬዚደንት በሶስት ሺህ ብር ደሞዝ የትም አለም የለም። እና ዛሬ ለመታሰቢያ አንድ ፓርክ ቢሰራ እነዚ ሰልፍ ወጡ የተባሉ አደገኛ ቦዘኔዎች አቃጠሉ አሉ። ሀዘኔ መሪር ነው በእውንት ከሆነ። መለስ ቢያየን ያፍርብናል። ራእይ ሰጥቶን ያ ሁሉ አይምሮ ጨምቆ አውጥቶ እኛ እንዲ ወደ ድንቁርና ስንሄድ ያሳዝነዋል። በቶሎ መንግስ ፀጥታ ሊያስከብር ይገባዋል። እነዚ ቦዘኔዎችም ለፍርድ መቅረብ አለባቸው።” ብላለች::
የቀድሞው ጠ/ሚ/ር ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የሰሞኑ ሕዝባዊ ቁጣ ለቤተሰቧና ለንብረቷ እንድታስብ ካደረጋት ቀጣይ እቅዷ ገንዘቧን አሽሽታ ወደ ሌላ ሃገር መፈርጠጥ? ይህ የሕዝብ ጥያቄ ነው::

fredag 11 december 2015

“መሬት ለአራሹ” ተረስቶ “መሬት ለካድሬ” – ከአምዶም ገብረሥላሴ


oromo
“መሬት ለኣራሹ” የሚል 60ዎቹ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች መፎክር ነበር።
የጃንሆይ ዙፋን መገርሰስ ዋነኛ ምክንያት ሆነ። ደርግም ጥያቄው ህዝቡ በሚፈልገው መልኩ ኣልመለሰውም።
ህወሓት ደርግ ገርስሶ 4 ኪሎ ከገባ በኋላም የመሬት ጥያቄ “መሬት የህዝብና መንግስት ናት። መንግስት ማለት ህዝብ ሰለ ሆነ እኔ ራሴ የመሬት ባለቤት ነኝ” ብሎ በማወጅ ህዝባችን መሬት ኣልባ ኣደረገው።
“መሬት ለኣራሹ” ትቶ መሬት ለካድሬ የሚል ውስጣዊ መፎክር ለ25 ዓመታት ተግባራዊ ኣድርገዋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ እስቲ ሰሞኑ በውቕሮ የተጋለጠ ጉድ እንደምሳሌ ላቅርብ።
የውቕር ከተማ ከንቲባ ኣቶ ዘርኡ ገብረመስቀል እያሉ ኣቶ ገብረዝሄር ገብረመድህን የተባሉ ባለ ሃብት “ማድያ ለመክፈት ስለምፈልግ በኣውራ ጎዳና መስመር መሬት ይሰጠኝ” ኣሉ።
ማድያ እንዲሰሩበት የመረጡት መሬት 1200ካ/ሜ ሲሆን በውቕሮ ከተማ ገበያ ለካሬ ሜትር 700 ብር በሊዝ ገበያ የተወሰነለት ነው።
ባለሃብት በሊዝ ዋጋ ከገዛው 840 000 ብር መክፈል ነበራቸው ይሁን እንጂ ይሄ ብር ከመክፈል ከውቕሮ ከንቲባ ኣቶ ዘርኡ ገብረመስቀል ጋራ ተደራደሩ በድርድራቸውም ስምምነት ላይ ደረሱ። ከከንቲባው ጋር 4 ሰዎች ከባለ ሃብቱ ተደራደሩ።
oromo2
በድርድሩ ወደ መንግስት ካዝና ሊገባ የነበረውና በባለሃብቱ ሊከፈል የታሰበው 840 000 ብር ግማሹ እንዲቀርና ግማሹም ለኣምስት ሰዎች እንዲካፈሉት ወሰኑ። በዚህ መሰረት
1) ኣቶ ዘርኡ ገብረመስቀል 250 000 ብር
2) ምክትል ከንቲባ ገብረመድህን ስዩም 70 000
3) ተኽለ ኣብርሃ የመሬት ማልማት ፅፈት ቤት ሓላፊ( መዛገጃቤት) 50 000 ብር
4) ጊደና በርሀ የውቅሮ መሃንዲስ 50 000 ብር ተካፈሉት።
በዚህ መሰረት ኣቶ ገብረዝሄር ገብረመስቀል ሊከፍሉት ከነበረው ዋጋ በግማሽ ቀንሰው ለካሬ ሜትር በ23 ብር 420 000 ብር ለባለስልጣናት በመክፈል ከግማሽ በላይ ቅናሽ ኣግኝተዋል።
ሰሞኑ በትግራይ የህወሓት ካብኔ ኣባላት ግምገማዎች እያካሄዱ ይገኛሉ። በስብሰባው የተለያዩ ኔትወርኮች ያሉት ሲሆኑ ራስ በራስ እየተጠላለፉ ይገኛሉ።
በውቕሮ ከተማ እየተካሄደ ያለው ግምገማ የካቢኔ ባለስልጣናት ይሄ ሙስና ኣጋለጡ። በዚህ መሰረትም ከንቲባው ኣቶ ርኡ፣ የማዘጋጃቤት መሬት ማልማት ሓላፊ ተኽለ ፣ የውቕሮ ከተማ መሓንዲስ ጊደና በርሀ ሲታሰሩ ምክትል ከንቲባ ገብረመድህን ስዩም 70 000 ብር ሙሰኛ ባልታወቀ ምክንያት ኣልታሰረም።
መሬቱ ከኣራሹ ተቀምቶ ለካድሬው ጥቅም እየዋለ ይገኛል።
ኣቶ ሓየሎም በላይ 1200 ካ/ሜ መሬታቸው በከንቲባና ባለ ሃብቱ ያለ ካሳ ክፍያና የመሬት ልዋጭ ተነጥቀዋል። ኣብየቱታቸው እስከ ዞን ድረስ ቢያሰሙም ምንም መፍትሄ ኣልተሰጣቸውም።
tigrai
በተያያዘ ዜና የመቐለ ከንቲባ ነበርና የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባል የነበሩ ጉምቱ ባለ ስልጣንም ደብሪ በተባለ የገጠር ቀበሌ በሚስታቸው ስም ከኣንድ ገበሬ መሬት ቀምተው ኣርሶ ኣደሩ መሬት ኣልባ ሲያደርጉት ከቀበሌ እስከ ክልል ኣብየት ቢል ሰሚ እንዳላገኘ በሓድነት ክፍለ ከተማ በህዝብ ግምገማ ተጋልጠዋል።
የኣይናለም፣ እግሪሓሪባ ወዘተ ገበሬዎች በካድሬዎችና ባለስልጣናት ያለኣግባብ መሬታቸው እመተቀሙ መሬት ኣልባ ሁነዋል።
እንደነ ወይዘሮ ኣልጋነሽ ገብሩ የመሳሰሉ ጀግኖች ደግሞ መሬታችን ኣሳልፈን ኣንሰጥም በማለታቸው ለእስር ተዳርገው ይገኛሉ።
ይሄው ኣርሶ ኣደሩ ባገሩ መሬት ኣልባ ሲሆን ካድሬው ግን ከገበሬው እየቀማ ባለሃብት እየሆነ ነው።
የኦርሞ ህዝብ “የኣዲስ ኣበባ ማስፋፍያ ማስተር ፕላን ገበሬው መሬት ኣልባ ያደርግብናል” በማለት እየተቃወመው ይገኛል። ይሄ ተቃውሞ ከ25 ዓመታት የኢህኣዴግ ኣገዛዝ ልምድ ተነስተን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊደግፈው ይገባል።
መንግስትም ህዝቡ ያልተቀበለው እቅድ በመሰረዝና ሰልፉ ለመበተን የተጠቀመው ያልተመጣጠነ የሃይል እርምጃና ላደረሰው ጉዳት በድፍረት ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባዋል።
ኢህኣዴግ የመሬት ፖሊሲዎቹ መቀየር ኣለበት። መንግስት የኦሮሞ ህዝብ ሰለማዊ ተቃውሞ በኣግባቡ መመለስ ብቻ ሳይሆን ከመሬት ባለቤትነቱም መራቅና የማስተዳደር ስራ ብቻ እንዲታቀብ እንመክረዋለን።
ህወሓትና የትግራይ ህዝብ መለየት ያቃታቹ የህወሓት ካድሬዎችና ፅንፈኛ በጥላቻ ዓይናቹ የታወረው ተቃዋሚዎች ኣትድከሙ።
የትግራይ ህዝብ ከኦሮሞና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ጎን በኣንድነት ተሰልፎ ለውጥ እውን ያደርጋል። ህዝባችን በተግባር የሚደግፈው ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንጂ በስሙ የሚነግድለት ኣምባገነን ስርዓት ኣያስፈልገውም።
ነፃነታችን በእጃችን ነው።

የአጋዚ ሰራዊት በምዕራብ አሪሲ አዳባ ከተማ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ – አንድ ወጣት መገደሉ ተሰማ

adaba
(ዘ-ሐበሻ) በምዕራብ አሪሲ አዳባ ከተማ ለሰላማዊ ሰልፍ በወጡ የህብረተሰቡ ክፍል ላይ የአጋዚ ጦር ወታደራዊ እርምጃ መውሰዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ:: በከተማዋ የአጋዚ ጦር በወሰደው እርምጃ የጥይት ድምጽ እና ጭስ ከተማዋን ሞልቶት እንደዋለ ነዋሪዎቹ አስታውቀዋል::
እንደ ነዋሪዎች ገለጻ ከሆነ በአዳባ ከተማ በአጋዚ ጦር በተወሰደው ወታደራዊ እርምጃ አንድ ወጣት ተገድሏል:: በአዳባ የተገደለው ወጣት ስም ነስረዲን መሀመድ እንደሚባልም ታውቋል::
በአሁኑ ሰዓት ወደ አዳባ ከተማ መግባትም ሆነ መውጣትም የማይቻል ሲሆን ወታደሮች ከተማዋን አጥረዋታል:: በአጋዚ ጦር ጥቃት የቆሰሉት ወገኖች በሃዋሳ እና ኩረያ ሆስፒታል እያታከሙ መሆኑም ተሰምቷል::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48998#sthash.gn7pTMza.dpuf

በኦሮሚያ ዛሬ ብቻ የተገደሉት ወጣቶች ቁጥር 5 ደረሰ


oromo brother
(ዘ-ሐበሻ) ሁለተኛ ሳምንቱን የያዘውና በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች እየተደረገ ያለው ከባድ ተቃውሞ እንደቀጠለ ባለበት በዚህ ሰዓት በአጋዚ ጦር ዛሬ ብቻ የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ወደ 5 ማደጉ ተገለጸ::
oromo
ከተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች እየመጡ ያሉት መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ በፌደራልና አጋዚ ጦር በኢናንጎ ከተማ 3; በባኮ ከተማ 1 እንዲሁም በባቢቺ ከተማ 1  ወጣት (የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያድግ ይችላል) ተገድለዋል::

ለዘ-ሐበሻ በደረሰው መረጃ በአምቦ ሆስፒታል በቁስለኞች ተጥለቅልቋል::
በአጋዚ ጦር ተጎድተው በአምቦ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ከሚገኙት መካከል
1ኛ ታመን ውቤ ደምሰው
2ኛ ዓለሙ ለማ
3ኛ. ፍጹም አየለ
4ኛ. ሽመልስ ዘሪሁን
5ኛ ማሙሽ ሃያሉ
6ኛ ገመቹ ሃሬርሳ
7ኛ ሚሚ ቶሎሳ እንደሚገኙበት ታውቋል::
እንደዚሁም በጅማ ሆስፒታል ቁሰለኞችን ሲያክሙ የቆዩ የህክምና ባለሙያዎች ሳይቀሩ ተቃውሟቸውን ማሰማት ጀምረዋል::
በሌላ ዜና የአዲስ አበባ እና የጂማ መንገድ መዘጋቱን የሚገልጹት ዘገባዎች በዲላ ከተማም እንዲሁ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ እየተደረገ ነው ብለዋል:: በተቃውሞው የተነሳ መንገዱ በመዘጋቱ መኪኖች በጠቅላላ ቱሉቦሎ ላይ ቆመዋል::
በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን የሕዝብ ቁጣ ለማብረድ የፌደራል ፖሊስ እና የአጋዚ ጦር በየአካባቢው ያሉ የነዋሪዎችን ጭነት መኪናዎች አስገድደው በመውሰድ ሰራዊት በመጫን ሕዝብ ለመጉዳት እየተጠቁመበት እንደምገኙ የአይን እማኞች ይናገራሉ::
ዘ-ሐበሻ በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን የሕዝብ ቁጣ እየተከታተለች መዘገቧን ትቀጥላለች::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48927#sthash.XVWvJODD.dpuf

በሚኒሶታ ፍቅር ያሸነፈበት ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ



(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ የሚገኘው የኦሮሞ ማህበረሰብ ነበር በቅድሚያ ይህን የኦሮሞ ተማሪዎችን ጥያቄ ለመደገፍ ሰላማዊ ሰልፍ የጠራው:: ይህን ተከትሎ በሚኒሶታ የሚገኘው የኢትዮጵያ ወጣቶች ንቅናቄ ሰልፉን እንደሚቀላቀልና ሰላማዊ ሰልፉን ደግፉ ከኦሮሞ ወንድም እና እህቶቹ ጋር እንደሚቆም መግለጫ አወጣ::
Ethiopia Minnesotaethiopia minnesota 3ethiopia Minnesota2
ይህ ሰልፍ በሰፊው ሚኒሶታ የአንድነት ምላሽ ማግኘቱን የተረዱና በኦሮሞ ሕዝብ ስም የሚነግዱ የሕወሓት መንግስት ተላላኪዎች ኢትዮጵያዊያኑን “በዚህ ሰልፍ ላይ የኢትዮጵያ ባንዲራም ሆነ ሌላ መል ዕክት ይዛችሁ መገኘት የለባችሁም.. ይህን ካደረጋችሁ ብጥብጥ ሊፈጠር ይችላል” የሚል ቅስቀሳ ማድረግ ጀመሩ:: ሆኖም እንዲህ ያለው ሕዝብ ሲገደል በአንድነት መቆም ሲገባ የሚያራርቅ ሥራ የሚሰሩት በኦሮሞ ሕዝብ ስም የሚነግዱ የሕወሓት መንግስት ተላላኪዎች መሆኑን የተረዱት ወገኖች ሰልፉን የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘው; የተላላኪዎቹን ማስፈራሪያ ወደጎን ትተው ጥያቄያችሁ ጥያቄያችን ነው በሚል ተቀላቅለውታል:: የሕወሓት መንግስት ተሸነፈ!!! ያሰበው ተንኮልና ሕዝብን ከሕዝብ የማራራቅ ተግባር በፍቅር ተሸንፏል::
ዛሬ በሚኒሶታ ስቴት ካፒቶል ደጃፍ ላይ ከቀኑ በ12 ሰዓት ነበር ይህ ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራው:: ሰልፉ በተጠራበት ሰዓት ዝናብ እየዘነበ ነበር:: ባሃገር ቤት ሕዝብ ላይ የሕወሓት መንግስጥ ጥይት እያወረደ እኛ ዝናብ ቢወርድብን ልንፈራ ነው ወይ? ያሉ የሰልፉ ታዳሚዎች ስቴት ካፒቶሉን አጥለቀለቁት::
በሰልፉ ላይ የኦሮሞ ማህበረሰብ; የኦጋዴን ማህበረሰብ እና የእናትየው የኢትዮጵያ ባንዲራም ተውለብልቧል:: ለሕወሓት መንግስት በኦሮሚያ ምድር ላይ ንጹሃንን መገደሉን እንዲያቆም; በልማት ስም ገበሬዎችን ራቁቱን እያስቀረ መሬት መቸብቸቡን እንዲያቆም; ብሎም ያን ምድር ለቆ እንዲወጣ ተጠይቋል:: የአሜሪካ መንግስትም ከሕወሓት መንግስት ጋር እንዳይተባበር ሕዝቡ አምርሮ ጠይቋል::
Minnesota ethiopia
ሰልፉ እየተደረገ ባለበት ወቅትም ወንድማማች የሆኑ ሕዝቦች በአንድ ላይ የተለያዩትን ባንዲራዎች በአንድ ላይ በመያዝ ለመጀምሪያ ጊዜ የአንድነት ፍቅር የተሞላበት ፎቶግራፎችን ሲነሱ ነበር:: በሚኒሶታ እንዲህ ያለውን ፍቅር እና አንድነት ለመመስረት ከፍተኛ የሆነ መስዋዕትነት እየተከፈለ ባለበት ሰዓት የሕወሃት መንግስት ተላላኪ የሆኑ ወገኖች በኦሮሞ ሕዝብ ስም ከኦሮሞ ሕዝብ ጎን እንቆማለን የሚሉትን ስም እየሰጡ የማንጓጠጥ ሥራ መስራታቸውን የማቆሚያ ጊዜው አሁን እንደሆነ ይህ ሰልፍ አሳይቶናል::
ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያውያን በሊቢያ ሲገደሉ አዝኖ እዚሁ ዛሬ ሰልፍ የተደረገበት ቦታ ላይ የወጡ ሁሉ ዛሬም እዚሁ ነበሩ:: በሞቱት ወገኖች ብናዝንም አንድነትና ፍቅራችንን በመመለሱ ደግሞ እንኮራለን::
በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ከሰልፈኞቹ እንደተነገረው የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ መብቱ እንዲከበርለት መጠየቅ እንጂ ከየትኛውም ብሄር ብሄረሰብ ጋር ለመጋጨት አይደለም:: አንዱን ከሌላው ለይቶ ከዚያ መሬት እንዲሰናበት መጠየቅ አይደለም::

የአ. አበባን ማስተር ፕላንን በመቃወምና ለተገደሉት ተማሪዎች አጋር ለመሆን በአውስትራሊያ ቪክቶሪያ የተደረገ ሰላማዊ ሰልፍ - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48979#sthash.v5k3VlsE.dpuf


በቪክቶሪያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ማኅበር አባላት፤ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላንን በመቃወምና ኦሮሚያ ክልል ውስጥ በተካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎች ሳቢያ ህይወታቸውን ላጡት ወጣቶች ድጋፋቸውን በመቸር ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል። የተቃውሞና የድጋፍ ሰልፉ የተካሄደውም ዓርብ፤ ዲሴምበር 11 2015 ሜልበርን ከተማ ውስጥ ነው።

የአ. አበባን ማስተር ፕላንን በመቃወምና ለተገደሉትን ተማሪዎች አጋር ለመሆን በአውስትራሊያ ቪክቶሪያ የተደረገ ሰላማዊ ሰልፍ | Audio

በአንዋር መስጊድ የፈነዳው ምንነቱ ያልታወቀውን ፈንጂን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ


  • 320
     
    Share
anwarከቢቢኤን ራድዮ የተገኘው ተጨማሪ መረጃ እንደሚያመለክተው በዛሬው ዕለት በታላቁ አንዋር መስጊድ የፈነዳው ያልታወቀ ፈንጂን ደህንነቶች የ ኤሌክትሪክ ፍንዳታ ነዉ የሚል የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ ነዉ ሲሉ እማኞች ገልጸዉልናል ብሏል:። ራድዮው ምንጮቼ ገለጹልኝ እንዳለ መዉሊድን አስመልክቶ ይበተን ከነበረ ከረሜላ ጋር አብሮ በሶፍት ወረቀት የተጠቀለለ ነገር ሰዎች ላይ ወድቆ ነዉ ፍንዳታዉ የተከሰተዉ።
ራድዮው እንደዘገበው ከሰዉነት ላይ የተቆረጠ ስጋ የፈሰሰ ደም ያለበት ፎቶ ግራፍ በሶሻል ሚድያዎች የተለቀቀ ሲሆን ፍንዳታዉ እንደተከሰተ ደህንንነቶች ግቢዉን የመቆጣጠራና የማጽዳት ስራ ላይ ነበሩ። ግቢዉ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዉሉ ከተጠረገ በሗላ ከጠረጋ የተረፈ የሰው ስጋ (ሙዳ ስጋ)አግኝተዉ ፎቶ ማንሳታቸዉን እማኞቻችን ነግረዉናል ሲል ራድዮው ዘገቧል::
በዚህ ምንነቱ ያልታወቀና ከወደላይ ተወርውሮ የመጣ ነው በተባለው ፈንጂ የተነሳ 6 ሰዎች ቆስለው ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ህክምና ላይ ናቸው::
1 የሞተ ሰውም አለ እየተባለ ሲሆን ዘ-ሐበሻ ይህን ለማጣራት እየሞከረች ነው::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48988#sthash.VjwMozQg.dpuf